Tuesday, August 22, 2017

የመጽሐፍ ምርቃት ግብዣ


ብዙ የግጥም ውድድሮች አሸናፊ የሆነው ዘነበ ታምራት ከረጅም የሕይወት ልምድ በመነሳት እነሆ ግጥሞቹን ለአንባቢያን በትህትና ያቀርባል። ግጥሞቹ ስር ሰደድ ማሕበራዊ ችግሮችን በማንሳት ትችቶችን፤ እርማቶችን በምክር፤ በግሰጻ፤ በማሳመን በማባበልም ጭምር ጥልቅ መፍትሄዎችን ጠቅልለው ለምግበ-አእምሮ ያቀርባሉ።

እያዝናኑና እያሳሳቁ ቁም ነገር ያስተምራሉ። የዘመናችንን የማህበራዊ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ በነገረ-እርክሪቲክመልክ ለመጭው ትውልድ ትምህርት ይሆኑ ዘንድ ያስተላልፋሉ።

የመጽፏ ዓላማ ልምዱ እይተለወጠና እየከፋ በመሄድ ላይ ያለውን የሕብረተሰባችን አስከፊ ገጽታ  ሃይ ብሎ ለመመለስ፤ የአስተዳደር በደልን በምክርና በግሳጼ ለመቅረፍና በሕግ የበላይነት የሚተዳደር ሕብረተሰብ እንዲፈጠር መገፋፋት ነው።



የመጽሐፍ ምርቃት ግብዣ
________________________________________________________
የማክበር ሰላምታዬን እያቀረብኩ “የሰው ሰውነቱ” በሚል ርእስ ያቀረብኩትን “የቅኔ ማዕበል“ መጽሐፍ ሴፕቴምበር 3 ቀን 2017 ዓ/ም 3.00 PM በመሶብ ሬስቶራንት አዳራሽ ስለማስመርቅ በቦታው ተገኝተው የምርቃቱ ተካፋይ እንዲሆኑ በማክበር ጋብዤዎታለሁ።
ከልብ ከመነጨ ሠላምታ ጋር
ዘነበ ታምራት ገብረማርያም
የዝግጅቱ ቦታ አድራሻ
መሶብ የኢትዮጵያ ባሕል ምግብ ቤት
1041 S. Fairfax Ave.
Los Angeles, CA.90019
Tel. 323 938 8827
አቶ ዘነበ ታምራትን ለማግኘት ከፈለጉ
ቴሌፎን 310 774 6007
e-mail ztamira@ yahoo.com             
የመጸሐፉ ዋጋ $ 12.00 ብቻ



Ethiopian Flag Coloring Page - Viewing Gallery

No comments:

Post a Comment