Saturday, June 24, 2017

አማራ መደራጀት ጉዳይ/አቻምየለህ ታምሩ



”አገር ማለት በኢትዮጵያን አገላለጥ ከብሄር እስከ ጎጥ የሚካተት ጂኦግራፊያዊ ቦታ ነው። አንድ ሰው በተለምዶ የትውልድ ቦታ "አገሬ“ ሲል ይስተዋላል ወይንም ሊል ይችላል። አገርህ የት ነው? ጎንደር (ክ/ሃ)ወይንም ከዛ አሳንሶ ደብረ ታቦር እንዲሉበህግ ግን አገር ማለት አንድን ሰው ዚግነት ሰጥቶት የዜግነት መብቱን የሚያስከብርለት ባለመብቱም በዜግነቱ ግብር የሚገብርለት የጆግራፊ ቦታ ባለቤት አካል ነው። ኢትዮጵያውያን ዜግነታቸው የሚከበረው በኢትዮጵያ ነው። ስለዚህ የትውልድ ስፍfራቸው የትም ይሁን የት አገራቸው በህግ "ኢትዮጵያ“ ነች። በፖለቲካ ሳይንስ አተናተን አገር አገር ለመባል ማሟላት ያለባቸው ሁኔታዎች አሉ። እዚያ ዝርዝር ውስጥ አልገባም። ነገር ግን ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥዋ ተለይቶና ታውቆ በተመድ የተረጋገጠላት አገር ነች። አማራ በኢትዮጵያ ክፍላተ ሃገራት ተሰራጭቶ የሚኖር ጎሳ ነው። ብዛቱና፡ በአገሪቱ ላይ ያለው የፖለቲካ ተጽእኖ እጅግ ሃያል ነው። ዜግነቱን የምታረጋግጥለት ”ኢትዮጵያ“ ስለሆነች አማራ ”ኢትዮጵያዊ“ ነው።“ (ተመዘዘ ስይፉ)


ReplyJust now


አማራ መደራጀት ጉዳይ
በአቻምየለህ ታምሩ
ከሰሞኑ የአማራው በአማራነት መደራጀት ጉዳይ እንደገና ተቀስቅሶ የውውይት አጀንዳ የሆነ ይመስላል። ገራሚው ነገር የአማራውን በአማራነት መደራጀት አጀንዳ እያደረጉ ያሉት ሰዎች በዘውግ ከተደራጁት ቡድኖች ጋር አብሎ ለመስራት ደፋ ቀና እያሉ ያሉ ግለሰቦች ጭምር መሆናቸው ነው። የአማራው በአማራነት መደራጀት ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም። ሆኖም ግን የአማራውን በአማራነት መደራጀትና «የአማራ ብሔርተኛነት» የሚባለውን የሌለ ነገር መለየት ያስፈልጋል። እኔ እስከሚገባኝ ድረስ የአማራ ብሔርተኝነት የሚባል ነገር የለም። የአማራ ብሔርተኛነት ኢትዮጵያዊ ብሔርተኛነት ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ መኖር ያለበትና ሊኖር የሚገባው ኢትዮጵያዊ ብሔርተኛነት ብቻ ነው። ብሔር የግዕዝ ቃል ነው። ትርጉሙም አገር ማለት ነው። ብሔር የሚለው የግዕዝ ቃል ከህዝብ ጋር የሚያገናኝው ነገር የለም። ብሔር የሚገልጸው ምድሩን ነው። በእንግሊዝኛም ብሔር ማለት Nation ማለት ነው። United Nations የአገራት ህብረት ማለት ነው።
ያ ትውልድ ነገድን ብሔር ወይንም Nation የሚል ስያሜ ሰጥቶ ፖለቲካ ያካሄደው «ዳግማዊ ምኒልክ የተባለ የአማራ ንጉስ የተለያዩ አማራ ያልሆኑ «የአፍሪካ አገሮችን» ከኢምፔሪያሊስቶች ጋር በመመሳጠር ወርሮ በቅኝ ግዛትነት ይዟል» የሚለውን የትውልዱን የትግል መነሻ ጽንሰ ኃሳባዊ መሰረት ለመስጠት ነበር። በያ ትልውድ ፍልስፍና አማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬ፣ ሲዳማ፣ ሶማሌ፣ ወዘተ ብሔሮች ወይንም Nations ስለሆኑ የዛሬዋ ኢትዮጵያ የአገራት ህብረት ወይንም United Nations ናት ማለት ነው። በያ ትውልድ የፖለቲካ ትርጓሜ ኒዮርክ ባለው አለማቀፉ United Nations እና በUnited Nations [of Ethiopia] መካከል ልዩነት የለም።
ማንም ያድርገው ማን ብሔሮች ወይንም ብሔረሰቦች የሚባሉት ስብስቦች በነገዳቸው ዙሪያ የሚያደርጉት የብሔርተኛነት ትግል ጸረ ኢትዮጵያዊነት ነው። ይህ ጸረ ኢትዮጵያዊነት ትግል ወያኔ፣ ኦነግ፣ ኢሕአፓ፣ መኢሶን፣ ወዘተ የታገሉለት አይነት ትግል ነው። ወያኔ፣ ኦነግ፣ ኢሕአፓ፣ መኢሶን፣ ወዘተ የታገሉት ዋለልኝ በፈጠረው እስር ቤት ውስጥ የታጎሩት «ብሔር፣ ብሔረሰቦች»፤ ምኒልክ ከኢምፔሪያሊስቶች ጋር ተባብሮ አፍሪካን ሲቀራመት ከጠቀለለበት ኢትዮጵያ የምትባል እስር ቤት «ነጻ ወጥተው» ኦሮምያ፣ ትግራይ፣ ኦጋዴን፣ አፋር፣ሲዳማ፣ ወዘተ የሚባሉ አዳዲስ የምስራቅ አፍሪካ አገሮች እንዲመሰረቱ ነበር። የዚህ ትግል ግብ ነጻነት ወይንም እኩልነት አይደለም። እንዴውም ይህ ትግል ከነጻነትና እኩልነት ጋር አንዳች የሚያገናኘው ነገር የለም። በአካባቢያችን የተካሄደ የነገድ ብሔረኛነት እንግስቃሴ ግብ ምን ሊሆን እንደሚችል ማወቅ የሚሻ የወያኔ፣ የኢሕአፓ፣ የኦነግና የሻዕብያ ትግል ፍሬ ውጤት የሆነችዋን የኢሳያስ አፈወርቁዋን ኤርትራ ማየት ይችላል።
የያ ትውልድ ድርጅቶች እነ ወያኔ፣ ኦነግ፣ ኢሕአፓ፣ መኢሶን፣ ወዘተ የታገሉት የራሳቸውን ባንዲራ ፈጥረው፤ የክብር ዘብ አሰልፈው የህይወት ዘመን ፕሬዝደንት ሆነው የሚገዘግዙት አገር መፍጠር ነው እንጂ ትክክኛ የህዝብን የመብት፣ የመናገር፣ የመወከልና የንብረት መብት ነጻነት ለማምጣት አይደለም። ለዚህ ቢሆን ኖሮ የታገሉት በየለቱ ንግግራቸውና ተግባራቸው ሁሉ በራስ ሀብት ስለማዘዝ፣ ስለመናገር፣ ስለመወከልና ስለንብረት ማፍራት መብት ነጻነቶች ሲሰብኩ ይሰማና ይታይ ነበር።
ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን «የኃሳብ ልዩነት የማያስተናግዱ ጨቋኝ» ብሎ ለነጻነት የታገለው ኦነግ ፋኖዎቹ የሚያነሱትን የኃሳብ ልዩነቶች መቀበል ተስኖት በቅድሚያ እነ ባሮ ቱምሳን ገደለ፤ ሲቀጥል ደግሞ እነ ሌንጮ ለታ አለን ያሉትን የሀሳብ ልዩነት ማስተናገድ አልችል ብሎ ሌንጮና በዙሪያው ያሉ ግለሰቦች ድርጅታቸውን ለማሻሻል ሀሳብ በማቅረባቸው የተነሳ ጠራርጎ በማባረር እነ ሌንጮ ለታ የኦነግ መሪዎች በነበሩበት ጊዜ እንደነ ጀኔራል ጃገማ ኬሎ አይነት ሀውልት ሊቀምላቸው የሚገባ የኦሮሞ ተወላጅ ኢትዮጵያውያንን «ጎበናዎች» እያሉ ሲያሸማቅቁበት የነበረውን የኦነግ ስድብ ወደራሳቸው አዞሮ ትናንትና እነ ሌንጮ እነ ጀኔራል አበራ አበበንና መርዕድ መንገሻን «ጎበናዎች» እያሉ ሲያሸማቅቁበት በነበረው የኦነግ ስድብ ዛሬ በተራቸው እነሱን «ጎበናዎች» እያለ ሲሰድብ የሚውለው፤ አንድ የነበረው ኦነግ ግለሰቦች የተለየ ሀሳብ ባነሱ ቁጥር እየተሰነጠቀ ዛሬ ላይ ለስምንት ተከፍሎ በየሳምንቱ ጥምረት ሲመሠርትና ሽር ብትን ሲል የሚውለው፣ የኦሮሞን ገበሬ ከመሬቱ ሲያፈናቅል ከሚውለው የትግሬ አገዛዝ ጋር ምርጫ በደረሰ ቁጥር «እንደራደር እያሉ» አገር ቤት ለመግባት የወያኔን ደጅ የሚጠኑት እድሜ ልካቸውን የታገሉት እንደ መለስ ዜናዊ ጮሌ የሆነ አንዱ ኦነጋዊ የህይወት ዘመን ፕሬዝደንት ሆኖ የሚገዘገዘው የኦሮሞ አገር ለመመስረት እንጂ የሀሳብ ልዩነት ለሚከበርበት ነጻነትና የኦሮሞ ገበሬ የመሬት ባለቤት የሚሆንበትን ሁኔታ ለመፍጠር ስላልነበረ ነው።
በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን የሀሳብ ልዩነት አልተከበረም ብለው የሀሳብ ልዩነት እንዲከበር ለመታገል ጫካ ገባን ያሉት ወያኔና ኢሕአፓም ልክ እንደ ኦነግ የታገሉት የራስ አገር ለመፍጠር እንጂ የሀሳብ ልዩነት እንዲከበር ወይንም ለነጻነት[for freedom] ቢሆን ኖሮ ወያኔ በየ አሥር ዓመቱ ለሁለት እየተከፈለ TAND, TPDM, ARENA, ወዘተ እያለ አይባዛም ነገር፤ ኢሕአፓም እንደ አሜባ ራሱን እየቆረጠ «ኢሕአፓ D» ምንትሴ እያለ እየተራበ እድሜ ልኩን ርስ በርስ ሲጫረስ አይኖርም ነበር።
ኢሕአፓ ከምስረታው ጀምሮ የታገለው ኢትዮጵያን በመበታተብ የዋለልኝ መኮነንን እስረኞች «ነጻ አውጥቶ» ከሰማኒያ በላይ የሚሆኑ አዳዲስ የአካባቢ አገራትን ለመመስረት ነበር። የኢሕአፓ አስተሳሰብ ውሉድ የሆነው ወያኔ ደግሞ ሻዕብያን ተከትሎ አዲስ አበባ ከገባ በኋላ ኢሕአፓ ሊመሰርታቸው የታገለላቸውን ከሰማኒያ በላይ በየነ መንግስታት ወደ ዘጠኝ ክልሎች በማጠፍ የትግራይን የበላይነት በሌሎችን ኢትዮጵያውያን ፍዳና መከራ ላይ ማደላደል እስከቻለ ድረስ እንዳሻው የሚያስገብራት፤ ነገር ግን በማንኛውም ጊዜ ዘጠኝ አገር ልትሆን የምትችል የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ስብስብ ፈጠረ። የኦሮሞ፣ የትግሬ፣ ወዘተ ብሔርተኛነት የወለደው ትግል አሁን ያጋመስነው እንደ ሕዝብ የመኖር እጣችን ለጊዜውም ቢሆን ጥያቄ ውስጥ የሚገባበት አሊያም የሚያቆምበት ደረጃ ላይ አድርሶናል። አማራው በታሪኩና በባህሉ ጥላቻ ስለሌለው የነ ኦነግ፣ ወያኔ፣ኢሕአፓና ወዘተ አይነት ደም የተጠሙ ድርጅቶች ትግል አያደርግም።
ከዚህ በፊት እንደተናገርሁት የአማራ ክልል ኢትዮጵያ ነች። የኦሮሞም ሆነ የሌሎች የኢትዮጵያ ነገዶች ክልላቸው ኢትዮጵያ ናት። አማራው የሚያደርገው ትግል በዚች በክልሉ በኢትዮጵያ ከሌሎች እኩል በጋራ ለመኖር ነው። የአማራ ብሔርተኛነት የመፍጠር ሕልም ይዞ ወያኔና ኦነግን መውቀስ ግብዝነት ነው። ትክክለኛው የፖለቲካ ትግል ሁሉም ኢትዮጵያውያን ማንነታቸውና ኃይማኖታቸው ተከብሮ፤ ቋንቋቸውን እየተናገሩ በዜግነት እኩል ሆነው የሚኖሩበትን አገር የመፍጠር እንቅስቅሴ ነው። ይህ አይነት ትግል ከነገድ ብሔርተኛነትጋር የሚያገናኝው ነገር የለም።
የሆነው ሆኖ አማራ እያካሄደው ያለው ትግል በሰፊዋ አገሩ በዜግነት እኩል ሆኖ ለመኖር የሚያካሄድ ተጋድሎ ወይንም የኢትዮጵያ ብሔርተኝነት ትግል እንጂ የአማራ ብሔር ወይንም Amhara nation ለመፍጠር አይደለም። የአማራ ብሔር ኢትዮጵያ ነች። የአማራ ወይንም የኦሮሞ ብሔርተኝነት የሚባለው እንቅስቃሴ ኢትዮጵያን አፍርሶ በሸምበቆ አጥር ተከልለው ርስ በርስ የሚተረማመሱ የአካባቢ መንግስታትን የመመስረት ጸረ ኢትዮጵያ ትግል ነው። ባጭሩ አማራ ከፍ ብለን እንዳየነው አይነት የከሰረ ትውልድ የነገድ ብሔርተኛነትን የትግል መመሪያው አድርጎ ትግል አያካሂድም።
ማንበብ ከብዙ ስህተት ያድናል። ባሌ ከጥንት ጀምሮ የአማራ ጭምር ርስተ ምድር የነበረ፤ ግራኝ አህመድ «የባሌ አበሾች ሰይጣኖች ናቸው» ሲል የመከሰረላቸው የባሌ ነጋሹ የራስ ተክለ ሃይማኖት ግዛትና ከግራኝ አህመድ ጋር ሲዋጉ ለአገራቸውና ለኃይማኖታቸው የወደቁት የባሌ ተወላጆች የነ ራስ ነብያንትና የነ አዛዥ ፋኑኤል መቃብር ነው። ደዋሮ [የዛሬው ምዕራብ ሐረርጌ] የልብነ ድንግል የጦር አዝማች የነበረው የቢትወደድ በድል ሰገድ ርስት ነው። ዳሞትና ቢዛሞ[የዛሬው ወለጋ] በሽምግልና እድሜው ግራኝን ለመፋለም ዘምቶ አስደማሚ ተጋድሎ ያደረገው የልብነ ድንግል የጦር አዛዥ የአዛውንቱ የራስ ወሰን ሰገድና የጀግናው ልጁ የባህር ሰገድ እትብት የተቀበረበት አገራችን ነው። ፈጠጋር[ የዛሬው አርሲ] እነ ነጋሽ ተክለ ሐዋርያት ከግራኝ ጋር ሲፋለሙ የወደቁበት ያያቶቻችን ርስት ነው።
ስለዚህ አማራው የሚጋደለው በአባቶቹ አገር በኢትዮጵያ እኩል ዜጋ ሆኖ ለመኖር እንጂ እንደ ወያኔና ኦነግ ለብሔርተኛነት አይደለም። ብዙ ሰው የአማራው በአማራነት መደራጀት ለወያኔ ስኬት ነው ብሎ ያስባል። ይህ በጣም የተሳሳተ ነው። አማራው በኢትዮጵያ ለመኖር የሚያደርገው ትግል የወያኔ ስኬት ሊሆን አይችልም። የአማራው በአማራነቱ መደራጀቱ የወያኔ ስኬት የሚሆነው የአማራው ትግል የአማራ ብሔርተኛነት ከሆነ ነው። አማራው ለብሔርተኛነት ከታገለ የሚታገለው ለኢትዮጵያ ብሔርተኛነት ነው።
አቻምየለህ ታምሩ
9 Comments
Comments
ድል ለአማራ ህዝብ አቻምየለህ ይህን ቢፅፍ ምንም አይደለም ከየትኛውም የፖለቲካ ድርጅት አስተሳሰብ ውጪ እንደመሆኑ በግለሰብ አቋምነት ስለሚያዝለት ከፅሁፉ ጋር መስማማት ወይም አለመስማማት ይቻል ይሆናል እንጂ ሌላ ተያያዥ ጉዳዮች ላይኖሩ ይችላል አቶ አንተነህ ግን የአማራ ብሄርተኛ ድርጅት አባልና አመራር ሆነህ ሳለ የአማራ ብሄርተኝነት የለም ካለም የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ነው… የሚልን ፅሁፍ ስታጋራን ምን ያህል ፖለቲካዊ አቋምህ እንደዋዥቀ ወይም ሲጀመርም ፖለቲካዊ አቋም እንደሌለህ አሳባቂ ነው። ሌላውን ለጊዜው ልተወውና የአማራ ብሄርተኝነት የለም ያለው ኢትዮጵያዊ… … ነው ብለህ ካመንክ ወይም ከተስማማህ ማንነትን መሰረት አድርጎ በተደራጀ ድርጅት ውስጥ ምን ታደርጋለህ? ጊዜህንና ጉልበትህን ስለምን ባላመንክበት የትግል መንገድ ታፈሳለህ? ያለው የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ከሆነ ለምን በአንድነት ጎራው ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር ተሰልፈህ አትታገልም? ቦታህን ያወቅህ አልመሰለኝም ብሄርተኛ ያልሆነ አማራ በአማራ ብሄርተኝነት ትግል ውስጥ ቦታ የለውም!!!!

Reply
9
June 22 at 4:44pm
ፅናቱ አማረ በዛም በዚህም ብየ ልረዳው ከምን አንፃር ብሄርተኛ እሚባል ነገር የለም እነዳለ ላየው ብሞክርም ሊገባኝ አልቻለም።የአማራ ብሄርተኝነት የለም የኦሮሞም የለም የኢትዮጵያ ግን አለ ማለት ምን እሚሉት ትርጓሜ ይሰጠው?? አንድን ጎሳ ብሄር ካላልን ምን እንበለው የኢትዮ ብሄርተኝነት ታዲያ እንዴት ኖረ በዚህ ትርጓሜ።ወይ እንደ ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ ብሄር ማለት ቋንቋ ነው እኔ አማራ ነኝ ኦሮሞ ነኝ ማለት ቋንቋየን ነኝ ማለት ነው ይበለን በዛ በኩል እንረዳ።ለማንኛውም እጅግ ይረደ ሊፈታ ሊተረጎም የማይችል እጅ እና እግር የለለው ፅሁፍ ነው ለኔ በግሌ አልገባኝ ሊሆን ይችላል የተረዳውት ግን እንደዛ ነው።

Reply
1
June 22 at 5:18pm
Temezeze Seifu "ጎሳ" tribe ነው “ ለምሳሌ “አማራ” ጎሳ ነው "ብሄር” አገር ነው ለምሳሌ ኢትዮጵያ አገር ናት በእንግሊዘኛው State, Country ወይንም Nation ልትባል ትችላለች

Reply1 hr
ፅናቱ አማረ ሀሀ ሰለዚህ 87 አገር አሉን ማለት ነው በኢትዮጵያ 😃?

Reply9 mins
ምኒልክ የአንጎለላ ዕንቁ ሰው አሁን እዚህ ላይ መኮመት እችላለው በነፃነት።
በመጀመርያ የአማራን መደራጀት በመቀበሉና ይህንንም ባዳባባይ በመናገሩ ላመሰግነው አወዳለው በመቀጠል ግን እኔ የአማራ ብሔርተኝነት የለም የሚለው አስተሳሰብ አማራ የለም ከሚለው አስተሳሰብ ጋር አንድ አይነት ሆነብኝ እና ግር አለኝ በዚህ ፅሁፍ ውስጥ እርስ በእርሳቸው የሚጣሉ አስተሳሰቦች ይታያሉ።
፦የአማራ መደራጀት ለምን? 

፦ብሔር ሀገር ማለት ነው ይለናል ልክ ነው ግን ሀገር ማለት እራሱ ምን ማለት ነው?
፦አንድ ህዝብ ሀገር አለኝ ወይም ይህ አገር የኔ ነው ለማለት የሚችለው ምን ሲሟላለት ነው?
፦አማራው በዚህ ሰአት በእርግጥ ሀገር አለው?
እነዚህ ጥያቄዎች ምናልባት ቢመለሱልን ደስተኛ እሆናለው።
ሌላው በዚህ ፅሁፍ ውስጥ ያየሁት የተንሸዋረረ እይታ የአማራን አደረጃጀት ወይም እንቅስቃሴ ከሌች ጋር ማነፃፃሩ ነው አማራ የራሱ በቂ የሆኑ ምክንያቶች እያሉትና ከራሱ ምክንይልት አንፃር መተንተን ሲገባ ከሌች እንቅስቃሴ ጋር በማስተያየት ለመተንተን መሞከሩ ስህተት ነው አማራ ማንንም አይቶ ወይም ከማንም ኮርጆ ይህን እንቅስቃሴ አልጀመረም።

Reply
3
June 22 at 6:46pm
Temezeze Seifu አገር ማለት በኢትዮጵያን አገላለጥ ከብሄር እስከ ጎጥ የሚካተት ጂኦግራፊያዊ ቦታ ነው። አንድ ሰው በተለምዶ የትውልድ ቦታውን "አገሬ“ ሲል ይስተዋላል ወይንም ሊል ይችላል። አገርህ የት ነው? go

Reply49 mins
Temezeze Seifu አገር ማለት በኢትዮጵያን አገላለጥ ከብሄር እስከ ጎጥ የሚካተት ጂኦግራፊያዊ ቦታ ነው። አንድ ሰው በተለምዶ የትውልድ ቦታውን "አገሬ“ ሲል ይስተዋላል ወይንም ሊል ይችላል። አገርህ የት ነው? ጎንደር (ክ/ሃ)ወይንም ከዛ አሳንሶ ደብረ ታቦር እንዲሉ። በህግ ግን አገር ማለት አንድን ሰው ዚግነት ሰጥቶት የዜግነት መብቱን የሚያስከብርለት ባለመብቱም በዜግነቱ ግብር የሚገብርለት የጆግራፊ ቦታ ባለቤት አካል ነው። ኢትዮጵያውያን ዜግነታቸው የሚከበረው በኢትዮጵያ ነው። ስለዚህ የትውልድ ስፍfራቸው የትም ይሁን የት አገራቸው በህግ "ኢትዮጵያ“ ነች። በፖለቲካ ሳይንስ አተናተን አገር አገር ለመባል ማሟላት ያለባቸው ሁኔታዎች አሉ። እዚያ ዝርዝር ውስጥ አልገባም። ነገር ግን ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥዋ ተለይቶና ታውቆ በተመድ የተረጋገጠላት አገር ነች። አማራ በኢትዮጵያ ክፍላተ ሃገራት ተሰራጭቶ የሚኖር ጎሳ ነው። ብዛቱና፡ በአገሪቱ ላይ ያለው የፖለቲካ ተጽእኖ እጅግ ሃያል ነው። ዜግነቱን የምታረጋግጥለት ”ኢትዮጵያ“ ስለሆነች አማራ ”ኢትዮጵያዊ“ ነው።

ReplyJust now
Anteneh Mulugeta በአማራነት ስለመደራጀት እና ኢትዮጵያዊነት

ሰሞኑን አንዳንድ የአማራው ትግል መሪዎች: አክቲቢስቶችና ጋዜጠኞች "ብአዴንን አትንኩብን" የሚል ውትወታ በሶሻል ሚዲያው ተደጋግሞ ስለታየ ብዙ ሰዎች የአማራ ድርጅቶች ወዴት እየሄዱ ነው? የሚል ጥያቄ እያቀረቡልኝ ነው:: 
...See More

Reply
2
June 22 at 7:33pm
ምኒልክ የአንጎለላ ዕንቁ ሰው አሁን አንተ በምትለን መልኩ ከሆነ የአማራን ትግል ወይም ብሔርተኝነት አትቀበልም ማለት ነው? ትንሽ ግር ስላለኝ ነው የአማራን ብሔርተኝነት ትግል የተረዳከው እንደ ሀገር አፍራሽ ነው ማለት ነው? አንተ ያለህበት ድርጅት ስለ አማራ ብሔርተኝነት ምን ይላል? AntenehMulugeta
አከለው አማራ አንድ የጎንደር አማራ ወጣት አንድ የባህር ዳር አማራ ወጣት ብትጠይቀው እነሱ ጋር አልኖርም ይልሀል።አንተነህ ከግንቦት ነው የመጣው አትፍረዱበት የሚበላ እንጅ የማይሰራ ድርጅት።
Dawit Tibebu አቶ አንተነህ ሁል ግዜ የአንድነቱ ሃይል በተናጋ ቁጥር ወቅት እየጠበቅህ እንደዚህ አይነት ነገሮችን ትፅፋለህ የተወሰኑት ጓዶችህም እንደዛው እስኪ አባት አገር አማራን እንመሰርት አለን ከሚሉት ውስጥ ብአዴንን አትንኩ ያሉ በስም አንድ ግለሰብ ጥራልን ?ሌላው ድርጅታችን ሁለት ነገሮችን ይዞ ይንቀሳቀሳል ብላችሁን ነበር ።
1/ፕላን A አማራው በአማራነቱ ተደራጅቶ በኢትዮጵያ መአቀፍ ሲሆን 2/ፕላን B 
...See More

Reply
2
June 22 at 9:14pmEdited
Begemdr Amhara ብአዴንን አትንኩብን የሚሉት ሰዎች እኮ ከቤተ አማራ ከድተዉ ከእናተ ጋር የተዋሃዱት ግለሰቦች እንጂ የአማራ ነፃ መንግስት እመሰርታለሁ የምትለዋ የትክክለኛዋ የቤተአማራ አባላትና አመራሮች አይደሉም ፡፡

Reply
1
June 22 at 9:51pm
Temezeze Seifu ውድ አቶ አንተነህ ሙሉጌታ የአማራን አደረጃጀት በተነሳ ያስቀመጥከው አንጀቴን አርሶታል እግዚአብሄር ይስጥህ። ስለ ሌላው አሳብህ መቼም ብትደውልልኝ ደግ ነው። አማራዊ ጥበብ ያስፈልገዋልና። የውይይቱን መነሻ የጻፈው ወንድማችን ስለ ብሄር ትርጉም የ1966 ፖለቲከኞች የሰጡት ትርጉም አሳሳች መሆኑን በተለይም ዋለለኝ ገና ትምህርቱን ሳይጨርስ ስለ ብሄር የሰጠው ኧትርጉዋሜ ሰፊውን ስእል የማያሳይና አባታችን ተስፋ ገብረስላሴ “ዘ ብሄረ ቡልጋ” እያሉ በፊደል መማሪያችን ላይ ይጽፉት በነበረው ላይ የተመሰረተ ይመስላል። የሚያሳዝነው የ 1966 ኮሚኒስቶችና ምሁራኖቻቸው ስህተቱን ተቀብለው በዚያው መንጎዳቸው ነው። አለበለዚያ የአቻሚለህ ትርጉም ከሰፊው ስእል እይታ ትክክል ነው። ስለዚህ ጉዳይ በአንድ የሳይበር ውይይት ላይ (6 አመት ገደማ ይሆናል) ተነስቶ ብሄር፤ አገር ጎጥና የመሳሰሉትን ትርጉማቸውን በመስጠት ምሁራን እንዲተቹበትና የዋለለኝ ስህተት እንዲታረም ያቀረብኩት 25 ገጽ ገደማ የሆነ ጽሁፍ ስላለ ይህን ጽሁፍ በግርድፉ አይተው ለመሰለቅና ለማስተካክል ወይንም ሃሳባቸውን ለመስጠት ለሚፈልጉ ማስተላለፍ እችላለሁ። አንተነህ የጠቀስከው የፕ/ር አስራት ሞዴል ዛሬ እኔ “አማራነት በኢትዮጵያዊነት" (The Amhara within") በሚል (የመአህድ ፖሊቲካል ቲዎሪ)የምሟገትበት ነው። ይህን ሞዴል የአንተ ሞዴል ማድረግህ አስደስቶኛል። ይህን ሞዴል ወስደን ያልተከፋፈለና የታጠቀ ጠንካራ የአማራ ሃይል በኢትዮጵያ ብሄረተኝነት ብናደራጅና ሁላችንም ብንረባረብ ወያኔ ባጭር ጊዜ ይጠፋል

Reply
1
Yesterday at 6:32pm
ምኒልክ የአንጎለላ ዕንቁ ሰው AntenehMulugeta ይህ የዶክተር ሰማኸኝ ጋሹን ትንታኔ እንዴት ታየዋለህ የህግ ምሁር እንደሆንክ እናውቃለን እሱም እንዳንተው የእግ ምሁር ነው 

ወንድማችን አቻሜለህ አንድ የሚያወያይ ሃሰብ ሰንዝሮአል። የአማራው በአማራነት መደራጀት ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም ካለ በሗላ የአማራ ብሔርተኝነት የሚባል ነገር የለም የአማራ ብሔርተኛነት ኢትዮጵያዊ ብሔርተኛነት እንደሆነ ገልጿል። በእንግሊ
...See More

Reply
1
June 22 at 9:20pmEdited
Tegegne Teshome I hope the issue is against the ideology of Bete Amhara not against other amhara political parties.
ኃያል ሰው አማራ ለማንነቱ ሲሰባሰብ፣ ለህልውናው ሲደራጅ ምነው ጫጫታው በረከተ? የአማራን ብሔርተኝነትን የለም ለማለትና ኢትዮጵያዊ ብሔርተኝነት ለማለት ለምን ተፈለገ? እውነት ሁሌም መራራ ልትሆን ትችላለች፣ እውነትን መቀበል ደግሞ አእምሮ ላለው ዜጋ ዋና ነገር ነው። እናንተ አማራው በግፍ በትር ሲቀጠቀጥ፣ ሲፈናቀል፣ ሲዋረድ፣ ሲታሰርና ሲገደል ድምፃችሁ ያልተሰማው ሲደራጅ ለመበታተን ያዙኝ ልቀቁኝ የምትሉት። አማራ ግን ወደ ኋላ ላይመለስ ወደ ፊት ጉዞ ጀምሯል። ነባራዊው እውነት ይህ ነው።

Reply
1
June 22 at 11:04pm
Kibrom Gedey It is agood analysis Acham go ahead
Makbel Dawit የ ፕ / ሮ ፍቅሬ ቶሎሳ አይነት፤ ገራገር ጹሁፍ ነው ማለት ይችላል ። በተለይ አንዳንዶች ገባ ብለን እንተንትን ብንል ፣ አስደንጋጭ ውጤት ነው የሚሰጡ ። ለማንኛውም አቻምየለህ የምወደውና የማደንቀው ልጅ ነው ። ባለህበት ሠላም ሁንልኝ ።

Monday, March 20, 2017

የቀድሞው የአሰብ ወደብ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አረፉ


የቀድሞው የአሰብ ወደብ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ መኮንን ተክለ አብ በአደረባቸው የጥቂት ቀናት ሕመም በድንገት አረፉ። የቀብራቸው ሥነ ስርአት ቤተ ዘመዶቻቸው፤ ወዳጆቻቸውና ጓደኞቻቸው እንዲሁም በሎስ አንጀለስ ነዋሪ የሆኑ ታላላቅ ኢትዮጵያውያንና ብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በሆሊ ክሮስ ሴሚታሪ ማርች 19 ቀን 2017 ዓ/ም ተፈጽሟል።

በቀብር ሥርአታቸው ላይ በተነበበው የሕይወት ታሪካቸው መሰረት አቶ መኮንን ተክለ አብ እንደ እ.አ አቆጣጠር በ1953 ዓ/ም በደሴ ከተማ ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ የአንደኛ ደረጃ ትምሕርታቸውን በንጉስ ሚካኤል ት/ቤት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በ ወ/ሮ ስሂን ት/ቤት ጨርሰው በአሰብ ወደብ አስተዳደር ዋና መ/ቤት ተቀጠሩ። በዚህ መስሪያ ቤት በማገልገል እያሉ ባሳዩት ጥረት ስኮላርሺፕ ተፈቅዶላቸው የተለያዩ የወደብ አሰተዳደር ኮርሶች በዩጎዝላቭያ በእንግሊዝና በአሜሪካን አገር በመሄድ ተካፍለዋል። እውቀታቸውን ለማዳበር ባደረጉትም ጥረት የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን አሜሪካን አገር ከሚገኝ ዩኒቨርስቲ አግኝተዋል። በመቀጠልም ሁለተኛ ዲግሪአቸውን እዚሁ አሜሪካ ከሚገኘው ከዴቭሪ ዩኒቨርስቲ ተቀብለዋል። አቶ መኮንን በስራቸው ላይ ባሳዩት ትጋትና ባስመዘገቡት ውጤት የተነሳ ከተራ ሠራተኛነትት ተነስተው የአሰብ ወደብታ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ለመሆን  በቅተዋል።

አመለ ሸጋው አቶ መኮንን ተክለ አብ በ1989 ዓ/ም ከባለቤታቸው ከ/ሮ አመለወርቅ ጋር ትዳር መስርተው እስከ እለተ ሞታቸው በፍቅርና በመተሳሰብ ለሌሎች ምሳሌ በመሆን ኖረዋል። ሟቹ አቶ መኮንን በነበራቸው የአገር መውደድ የተነሳ የአሰብ ወደብ በጠላት እጅ ሲወድቅ አሜሪካን አገር በስደት መኖር መርጠው ለ5 አመት ያህል በሎንግ ቢች የሎዝ አንጀለስ ወደብ ተቀጥረው ያገለገሉ ሲሆን እ አ አቆጣጠር ከ2001 ዓ/ም ጀምሮ እስከ እለተ እረፍታቸው ድረስ በጤና ዘርፍ የግል ድርጅት አቋቊመው አገልግሎት በመስጠት ላይ ነበሩ።

እኝህ ታላቅ ሰው ሕይወታቸውን በሙሉ እግዚአብሔርን ፈሪ ሰውን አክባሪ ተግባብተው ነዋሪ ነበሩ። ከዚህም በላይ ለቤተ ክርስቲያንና ለኢትዮጵያን ሕብረተሰብ ፈጥነው ደራሽ እንደነበሩ ይታወቃል። ሎስ አንጀለስ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያን አንድ ታላቅ ሰው አጡ። የዚህ ብሎግ አዘጋጅ የሆንኩት እኔ ዘነበ ታምራትም ሊተካ የማይቻል መካሪ ጓደኛዬን አጣሁ። መኴ እግዚአብሄር ነፍስህን ይማር!አንተ ብትሞትም እኛ ስለ ሰዎች ደህንነትና ስለ አገርህ አንድነት የነበረህን ቁጭት አንረሳውም። ለውድ ባለቤትህም መጽናናቱን ቸሩ አምላክ እንዲሰጣት የዘወትር ጸሎታችን ነው።

Thursday, February 16, 2017

አዬ ግም ፈረንጅ

     አዬ ግም ፈረንጅ  

                        ዘነበ ታምራት

አንድ ቀን በበጋ ከአልጋ ተነስቼ
ላፍታታ አከላቴን ጅምናስቲክ ሰርቼ
ስሷን ካናቴራ ከደረቴ አጥልቄ
ቁምጣዬን ታጥቄ
የስፖርት ጫማዬን ወደዛ ወርውሬ
እንደ አቤ ቢቂላ ልሮጥ በባዶ እግሬ
ያዙኝ ልቀቁኝ አልኩ ተነሳሁ ፎክሬ
ነገር ግን ሰው ሁሉ ጫማህን አርግ አለ
አለዚያ አትወጣም አይሆንም እያለ
በሩን አንቆ ይዞ መውጫ ከለከለ
እኔ ግን ልቀቁኝ በባዶ እግሬ ነው
ሮጬ እምመጣ እያልኩ ስከራከር
ሚስቴ ሰምታ ኖሮ ብቅ ብላ ወደ በር
“የምን ጋጋታ ነው እንዲህ ያለ ሽብር”
ብላ ብታባርቅ ቶሎ ተንደርድሬ
የስፖርት ጫማዬን በእግሬ ላይ ሸንቅሬ
አልኳት “እመቤቴ እሽ ውዷ ፍቅሬ”
ሰው ሁሉ ገረመው እንዲያ ስሽቆጠቆጥ
ለካ ላስቸጋሪም እንደዛ ለሚያብጥ
አለው ልክ አስገቢ ከወገቡ የሚንጥ
እያለ ታዘበ ወይ አለማወቁ
ያልቀመሰ ሁሉ የሚስት ምላስ ብርቁ
መለስ ስትልልኝ እኔም አልኩኝ ውልቅ
አድነኝ እያልኩኝ ከሚስት ምላስ ጅራፍ ከሴት ጋር ትንቅንቅ
ከውጭ እንደወጣሁ አልኩኝ ነጠር ነጠር
ዞር ስትልልኝ ጀመርኩኝ ልወጠር
ማንን እፈራለሁ ካለ እርሷ በስተቀር
ወዲያው ተያያዝኩት ኩስ ኩስ ማለቱን
ፊቴ የሚታየውን ዳገት ቁልቁለቱን
ኩስ ኩስ ያልኩትን የአሯሯጥ ስልት
በፈረንጅ አጠራር “ጆግ” ነው የሚሉት
ጆግ ሳደርግ ጆግ ሳደርግ ጆግ ሳደርግ ስሄድ
በቬነስ ጎዳና ስሮጥ ስራመድ
ፊቴም ላብ ለበሰ ሞቅ አለ አካላቴ
ደስታ ተሰማኝ ጋለ ሰውነቴ
ዳገቱን ወጥቼ ቁልቁሉን ወርጄ አራዳው ስደርስ
ፈርጥጥ ፈርጥጥ አለኝ እንደ አጉራ ፈረስ
እሮጥ እሮጥ እያልኩ ስመታ ገርዳሳ
አየሁ መናፈሻ ለአይን የሚያሳሳ
ከታች መደብ ሆኖ አረንጓዴ ሳር
ዙሪያው በአበቦች ተከቦ የሚያምር
አልፈው አልፈው ደግሞ ዛፎች ተተክለው
ይላሉ እረፍ  እረፍ የደከመን ሰው
ይሄ መልካም ስፍራ ቀልቤን ጎትቶት
ሩጫዬን አቆምኩ አረፍ ለማለት
እንዘፍ ብል አንዴ ከአረንጓዴው ሳር
ተመኘሁ አዛ ላይ ተኝቼ ማደር
ቀይ ሮዝ ነጭ ሮዝ የአበባ እምቡጥ
ሞልቷል ከዙሪያዬ ልብ የሚመስጥ
እጅግ ተመችቶኝ አልኩኝና እሰይ
በጀርባዬ ሆኜ ቀኝ ግራውን ሳይ
የገባሁ መሰለኝ መንግስተ ሰማይ
ትንሽ እንደ ቆየሁ በዚህ አኳዃን
ይሸተኝ ጀመረ ያልሆነ ጠረን
ይሄ እንግዳ ነገር እጅጉን ገርሞኝ
እጄን ለምርመራ ዃላዬ ላኩኝ
ቀዘቀዘኝ በጣም ተነሳሁ በርግጌ
       እጄ ካካ ዝቋል
       በካካ ተረፍቋል
ጀርባዬ በሙሉ በግም ተጨማልቋል
ቱታዬን ከኋላ ዞር ብዬ ባየው
የኩቲ  ካካ ነው ያጨማላቀው
ለካ መናፈሻው እንዲያ የሚያምረው
የኩቲዎች ካካ ሰገራ ቤት ነው
ታዘብኩት ፈረንጅን ሰከን ብዬ ሳየው
ላይ ላዩ እያማረ ውስጡ ለካ ግም ነው
ፈረንጅ ላዩ ያምራል
ብሉኝ ብሉኝ ይላል
እኛን ይጠየፋል
ግን ውስጡ ይከረፋል
የአሜሪካን ግቢ ያ የኛ ክርፋት
አለው ማስጠንቀቂያ ከሩቅ የሚሸት
የፈረንጅ ክርፋት ግን የአበባ ጥቅል
ኑልኝ ኑልኝ ይላል አዙሮ ሊጥል
በመሽፋፈኑ ይበልጠናል እንጂ
አዬ ግም! አዬ ግም! አዬ ግም ፈረንጅ!
    (የሎስ አንጀለሱ ገጠመኝ 06/16/2006)



Monday, November 7, 2016

The Mystery of my Independence


A Poem dedicated to Prof. Asrat Woldeyes
By Zenebe G. Tamirat
In the Horn of Africa where the mountains seem to meet the sky;
Along the shore of the sea that Mosses rolled on: and where the birds fly:
And down there where the obelisks are;
Where the river they call Awash crosses the land of the Afar; And,
Where the waters of the Nile are worshipped by Egyptians
Where the waterfall, they call, “Tis-Abay;”
Dreadfully Roars from its cliff to reach its bed
Where it is no more aggressive but just a friend: And then,
Boiled by the mystery sun that changes it into vapor,
Rises again so high;
There rests Abyssinia;
The country known as, Ethiopia!
The country that the Bible says, “Ethiopia stretches
 its hands, unto God:” And go forward in independence
For thousands and thousands of years,
And there in the midst, not only I,
But every walk of life before me,
Including mother of all mankind, Lucy,
Millions and millions of years ago were born in mystery.
And ever since, except those who left the land, everyone has been free.
Where I was born, everything used to be in a band;
The trees in the jungle stand,
So, thick side by side;
Allowing no passer-by to pass amidst them,
Even the wind could not have passed over,
Had it not whistled the national anthem!
With the wind whistling, leave alone the people,
The lions roar the sound of love,
And the tigers and the hypos, and the elephant dance,
The timid and the wild live in peace & relax,
Like birds of the same feather:
They walk together, they fly together and they eat together;
And when challenged they fight together!
Amazing beings! Amazing land!
So, fascinating, and so thrilling! So, wide and broad,
 A blessed gift of God!
So, now I am aware of the mystery of my independence!
I see! I see! It was the might of this oneness!
The filament of Ethiopian-ness
That threaded us together to enjoy,
The bond that clamped us long, long years ago until I was a little boy!
But later, revolted to forgo and go blind:
To say, “I am Eritrean, I am an Amhara, I am an Oromo, an Afar,
A Somali, a Guragie, a Benshangule: and lost deep in the wood.
Oh! My God aren’t we running wild?
Oh! My God! We have lost those days of Unity,
Brotherhood, fraternity, and sorority!
Can we not make it back once again to enjoy as Ethiopians?
Breaking the sufferance of ethnic-based miserable fragments?
And becoming one, once and only once?
·         (Dedicated to Professor Asrat Woldeyes, on the celebration of his 10th year of Memorial Day,  May 2009. Professor Asrat is a Martyr who lost his life fighting for the unity of Ethiopia)
·         The poet, Zenebe G. Tamirat is available @ ztamira@yahoo.com



Friday, October 28, 2016




                                                                   ሃገሬ


                 በ ገብረ ክርስቶስ ደስታ

አገሬ ውበት ነው

ለምለምና ነፋስ የሚጫወቱብት

አገሬ ቆላ ነው ደጋ ወይና ደጋ

እዚያ ብርሃን አለ ሌሊቱ ሲነጋ

 አገሬ ተራራ ሸለቆ ረባዳ

አገሬ ጂረት ነው ገደልና ሜዳ

ውሸት ነው በበጋ ጸሃይ አትፋጂም

ክረምቱም አይበርድም ................          

                      ለሙሉው ፎቶው ላይ ያለውን 3 ማእዘን ይጫኑ

Saturday, October 8, 2016

ኃይሉ ሻውል አረፉ






የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ ፕሬዚዳንት የነበሩት ኢንጅነር ኃይሉ ሻውል ባደረባቸው ሕመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው እአአ ኦክቶበር 8 ቀን 20016 ዓ/ም በ80 አመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው ለአመታት በወያኔ እስር ቤት ሲማቅቁ የነበሩት ኃይሉ ሻውል ይቅርታ እንዲጠይቁ ተገደው ከስር የተለቀቁ ቢሆኑም በንጽህና ጉድለትና በቅዝቃዜው ከታወቀው ከቃሊቲ እስር ቤት ይዘው የወጡት በሽታ ለሞት እንዳደረሳችው ተረጋግጧል። ይህ በሽታ እያሰቃያቸው ቢሆንም ኢንጅነሩ ወያኔንም በሽታውንም እየታገሉ እስክ ምርጫ 2005/2012 ድረስ መኢአድን በፕሬዝዳንትነት ሲመሩ ቆይተዋል።

የተከበሩ ኢንጅነር ኃይሉ ሻውል በአባይ ሸለቆ ጥናት፤ በአውራጎዳና፤ በሼል ኢትዮጵያ፤ በመተሃራ ስኳር ፋብሪካ ከተራ ሰራተኝነት እስከ ሥራ አስካሄያጅነት በደረሰ ደረጃ ያገለገሉ ሲሆን በደርግ ጊዜ የመንግስት እርሻ ሚንስትር በመሆን ሰርተዋል። ክቡርነታቸው የሚኒስትር ማዕረጋቸውን በፈቃዳቸው ከለቀቁ በኋላ በግል ሥራ ዘርፍ ተሰማርተው ሻውል ኮንሰልት የተባለ የአማካሪ ድርጅት በማቋቋም ከአገር አቀፍ እስክ ዓለም አቀፍነት አድርሰው ስፊና ልዩ ልዩ የልማት አገልግሎት እንዲስጥ አብቅተዋል።

በ1983 ዓ/ም በትግሬ ነጻ አውጭ ግንባር የሚመራው መንግስት አማራውን በብሄራዊ ጠላትነት ፈርጆ በመላው አገሪቱ የሚገኘው አማራ ላይ እሳት ሲጭር መላው አማራ “ሞረሽ!” ተብሎ ሲጠራ ኢንጅነር ኃይሉ ሻውል ጥሪውን ተቀብለው ወደ መላው አማራ ድርጅት በመቀላቀል በእሳት አደጋ ስራተኝነት  ሕዝብን ከጥፋት ለማዳን የተጀመረውን ርብርቦሽ በግንባር ቀደምት ነት ከሚመሩት አንዱ ለመሆን በቅተዋል። በፕሮፌሰር አስራት ወ/የስ በሚመራው በመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት  ውስጥ በምክትል  ፕሬዝዳንትነትና የውጭ ጉዳይ ሃላፊነት ሲያገለግሉ የቆዩት ኃይሉ ፕሮፌሰር አስራት በወያኔ እስርና ጥቃት ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ በምትካቸው ተመርጠው የመአሕድ ፕሬዝዳንት ሆነዋል። በዚህም ጊዜ በቀኛዝማች ነቅአ ጥበብ ሽምድምድና የደነቆረ አመራር ፈራርሶ የነበረውን መአሕድ በማቃናት የኢንጅነር ኃይሉ አመራር አስተዋጽኦ አድርጓል። ሆኖም ፓርቲው በብሄራዊነት እንዲያገለግል ታስቦ ወደ መላው ኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲነት ሲቀየር መአሕድ እንደገና በእነቀኝ አዝማች ነቅአ ጥበብ እጅ በመውደቁና የባሰ ተሽመድምዶ በመቅረቱ፤ የኢንጅነር ኃይሉ አመራር ከአዲስቹ የመአሕድ አመራር ጋር ቅራኔ ከመግባት ይልቅ በመተባበር ቢሰሩ ለአማራው ሕዝብ ትልቅ ተስፋና መከታ ይሆኑ ነበር የሚሉ ወገኖች ተከስተዋል። ቢሆንም መኢአድ ለአማራው ሕዝብ መብት ከመታገል አላቆመም የሚሉ ወገኖችም አልታጡም።

በ1997  ቅንጂት ሲፈጠር መኢአድ በመዋጡ ኢንጅነር ኃይሉ የቅንጂቱ ፕሬዝዳንት ቢሆኑም መሰረታዊ ፓርቲአችን መአሕድ አይፍረስብን  በሚሉ ጥቂት የፓርቲው አባላት ጥርስ ስር መግባታቸው አልቀረም። ይሁን እንጂ ቀደም ሲል ከመአሕድ ቀጥሎም ከመኢአድ አክራሪ አባላት የቀረበበትን ተቃርኖ በማክሽፍ የኢንጅነሩ አመራር እየገስገስ ሄዶ በኢትዮጵያ  ታላቅ ሕዝባዊ ኃይል ሆኖ በመውጣት ወያኔን ያንቀጠቅጥ ጀመር። በአገር ውስጥ ከሱማሌ ክልል ውጭ በስተቀር  ከሞላ ጎደል በሁሉም ክልሎች የተደራጀውና በዓለም ዙሪያ በተቋቋሙት የዲያስፖራ ድጋፍ ሰጭ ድርጅቶች ይረዳ የነበረው ቅንጅት በአብዛኛው የኃይሉ አመራር ውጤት ነው ማለት ይቻላል። ኃይሉ በአገር ውስጥ ከገጠር ወረዳዎች እስከ ክልል ዋና ከተሞች በመጓዝ ስለ ኢትዮጵያ አንድነት ሰበኩ። በአውሮፓ፤ በአሜሪካና በካናዳ በተደጋጋሚ በመዘዋወር አንድነት ኃይል መሆኑን አበክረው አሰታወቁ። የወያኔ አገዛዝም በዘር ላይ የተመሠረተ በመሆኑ አደገኛነቱን አስጠነቀቁ። በዚህም አመራራቸው ብቃታቸውን አረጋገጡ። በርሳቸውም አመራር ቅንጅት የ1997 ብሄራዊ ምርጫ አሸነፈ። ይሁን እንጂ ድሉ የተፈጸመው ዲሞክራሲ በሌለበት አገር በመሆኑ ውጤቱ ድል አድራጊው ወደ እሰር ቤት ድል ተነሽው ወደ ቤተ መንግስት ሆነ። ኃይሉም የዚሁ እውር ፍርድ ሰለባ ሆነው ከነወገኖቻቸውና የፖለቲካ ባልደረባዎቻቸው ጋር የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው ወህኒ ወረዱ።

ከእጅግ አሰልችና እልህ አስጨራሽ ትግልና ሕዝባዊ ውትወታ በኋላ ኃይሉና ባልደረባዎቻቸው ቢፈቱም ወያኔ በመሃላቸው ገብቶ በፈጠረው ልዩነት ቅንጅት ሲፈርሰ ኃይሉ መኢአድን እንደገና አደራጅተው ለ1997ቱ አገር አቀፍ ምርጫ አቀረቡ። ይሁን እንጂ ወያኔ የምርጫ ሥነ ስርአትን በተመለከተ ድርድር ውስጥ አስገብቷቸው የምርጫ ቦርድን ያላስተካከለ ውል በመፈረማቸው ከፖለቲካ ተቀናቃኞቻቸው አያሌ ተቃውሞ ደረሰባቸው። ይልቁንም በዚህ ምርጫ ወያኔ መቶ በ መቶ አሸንፍያለሁ በማለት ክአንድ በስተቀር ካለምንም ሌላ ተቃዋሚ ፓርላማውን በመሙላቱ ኃይሉ እጅግ ተማረው ከኢትዮጵያ ፖለቲካ አመራር ለመውጣት መወሰናቸውን በይፋ አስታወቁ። በፓርቲውም አመራር ተተኪ እስኪገኝ ቆይተው ስልጣናቸውን አስረከቡ።

ኢንጅነር ኃይሉ አልፎ አልፎ አመራራቸው በተቃርኖ (በ controversy)የታጀበ ቢሆንም በታታሪነታቸው፤ በግልጽነታቸውና በደፋርነታቸው የታወቁ መሪ ነበሩ። ለአገራቸው ያበረከቱት ወደር የሌለው  አገልግሎትም ስመ ጥር ኢትዮጵያዊ አድርጓቸዋል። ጥርሱን ካገጠጠ የትግራይ ወያኔ አምባገነን ጋር ያደረጉት ትግል በታሪክ ለትውልድ ሲተላፍ ሕያው ሆኖ ይኖራል። ደወል ለቤተሰቦቻቸው፤ ለወዳጆቻቸውና ለፓርቲያቸው መጽናናትን ትመኛለች።



                                                     


Friday, August 5, 2016

Press Release of the Orome Democratic Front (ODF)

On organization
The Central Committee of the Oromo Democratic Front (ODF) held an historical meeting from July 29 to August 4, 2016. The meeting was held at a time when people from all over Oromia were intensifying their uprising to demand democratic rights and genuine self-government in unison. The meeting recognized that the peaceful political struggle the Oromo people are waging inside the country is entering a new phase, gaining resilience and continuity.
ODF-Logo1
After listening to the organizational report presented by the Executive Committee, the Central Committee thoroughly discussed and reflected on the report. The Central Committee commended the Executive Committee’s effort and performance in implementing policies and carrying out day-to-day operations of the organization. The leadership took note of the strengths and weaknesses confronting the organization. A unified direction and steps were formulated to build on our strengths and also lessons were drawn from our weaknesses.
On Oromo protest
The meeting also assessed the political development in the Oromia region, and other regions, in Ethiopia.  Twenty-five years after it came to power, the Ethiopian People’s Democratic Front (EPRDF) neither democratized the country nor tackled developmental challenges facing our people. Massive violations of human rights and the prevalence of abject poverty continued to be features of EPRDF rule. Frustrated by the lack of democratic rights, good governance, and basic services, the protests instigated by the Oromo protest is now evolving into a country-wide mass uprising to demand fundamental democratic change.  Instead of addressing the legitimate demands of the various peoples, the regime chose to savagely attack its own citizens by killing, torturing, and incarcerating thousands of people. These desperate and cruel reactions by the regime against peaceful protesters proved to be futile as the yearning for change ignited in Oromia by the Oromo people is expanding to the other parts of the country, confirming the inevitability of change.
On the Gonder protest
The protest that started nine months ago in Oromia put the Oromo people in the front of the struggle for democratic change in Ethiopia. Now the movement has started to spread throughout the country. This week, a massive and spectacular nonviolent demonstration was held in Gonder. One of the historical significances of the protest in Gonder is the expression of unwavering solidarity with the struggle of the Oromo people and condemning the atrocities perpetrated against the Oromo by the cruel regime run by the EPRDF and dominated by the Tigrean People’s Liberation Front (TPLF), who have perpetrated extreme violations of human rights in the region. The demonstration of solidarity through nonviolent protests not only strengthens our peoples’ unbreakable bond but also speeds up and steers the country-wide movement, kindling the beginning of democratic change to be realized by consigning dictatorship in Ethiopia to dust bin of history. On this occasion, we call upon all the peoples of Ethiopia to defy the divide and rule policy of the regime and stand shoulder to shoulder in their struggle for democratic change and peaceful coexistence.
Call for the formation of Ethiopia-wide alliance
The Central Committee discussed in detail various initiatives the ODF has undertaken to reach out to various Ethiopian opposition groups and leaders. Recognizing that the relationship that has been cultivated with these groups is encouraging, the Central Committee instructed the Executive Committee to further strengthen the ties established in order to work toward the realization of an Ethiopia-wide coalition that can spearhead the nonviolent resistance engulfing the country. The coming together of various opposition groups not only speeds up the struggle by providing the most needed leadership, it also lays down the transition to democracy and peace. The ODF is happy to announce that it is working hard to materialize the Ethiopia-wide alliance and hopes to make public the end result of this effort in the near future. We also call upon all political organizations to be vigilant of the current political development in our country and come together to avoid any gap that the crumbling of the incumbent regime may create. United we will win, divided we will fail. The down fall of the EPRDF regime is certain. The question is not about if, but when. We need to play a constructive role by leading our peoples to democratic change. We cannot squander this opportunity as we have missed many of them in the past.
Call to international communities
The Central Committee calls upon international community to withdraw its financial and military support to the autocratic regime dominated by the TPLF in Ethiopia for a number of reasons. First and foremost, the regime is internally illegitimate, drawing support for its leadership only from external foreign powers rather than internal forces within Ethiopia. The United States and other members of the international community who are fighting extremism are undermining their own democratic values and long term security interests by continuing to support the incumbent regime. The United States is only compromising its long-term security interests by continuing to support an illegitimate and autocratic dictatorship in Ethiopia. Pressure must be put upon the TPLF/EPRDF to heed the demands of the people within the country they seek to rule, and the most effective way to influence the regime is pressure from external influential powers.

Justice and freedom for all!!
The Oromo Democratic Front Central Committee
August 5, 2016

 21 0
Share